እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረስዎ

   ክርስቶስ ተንሥአ ሙታን              ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ
   በዐብይ ኃይል ወሥልጣን              በታላቅ ኃይልና ስልጣን
   አሰሮ ለሰይጣን                        ሰይጣንን አሰረው
   አግአዞ ለአዳም                        አዳምን ነጻ አወጣው
   ሰላም                                 ሰላም
   እም ይዜእሰ ኮነ                       ከዛሬ ጀምሮ
   ፍሥሐ ወሰላም                       ደስታና ሰላም ሆነ

ሲፈጥረን ጀምሮ ዳር ድንበር የሌለው ፍቅሩ አስገድዶት በአመፃችን በበደላችን ከገባንበት የኃጢአት መቀመቅ ሊገላግለን እርሱ እራሱ በሞቱ ተቤዠን በሲዖል ተጥለው በአጋንንት ሲረገጡ የነበሩ ነፍሳትን ነፃ አወጣልን።

የትንሣኤው ነገር ለሰው ልጅ ህሊና ምጡቅ ነው በዕምነት ካልሆነ በሌላ መንገድ ተፈላስፎ መረዳት አይቻልሞ።

ለኛ ለክርስቲያኖች ግን የልብ ደስታን፤ የመንፈስ እርካታን የሚሰጠን አምላካችን ሞትን ድል አድርጎ ከመነሣቱም በላይ በስሙ ተጠምቀን ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን በእርሱ መንገድ እየተመላለስን ከዚህ ዓለም የምንጠራበት ጊዜ ሲደርስ ፈርሰን እንዳማንቀርና ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው በኃያሉ አምላካችን ፈቃድ እኛም በክብር ተነስተን ስሙን እየቀደስን ለዘለዓለም የመኖራችን ማረጋገጫ መሆኑ ነው።
(ሮሜ 6:5–9)

ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ ......