ልደቱ ደስታችን የተፀነሰበት ትንሣኤው ደግሞ ደስታችን የተወለደበት


ለእግዚአብሔር ክብር ይግባውና ሞት የማይገዛው ጌታችን በትንሣኤው የሞትን ሽንፈት፣ የመቃብሩን መረታት አረጋግጦ የእኛን ትንሣኤ ያበሰረን በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን በልደቱ የተጀመረው ደስታዋ በትንሣኤው ፍጹም መሆኑን ለማረጋገጥ ስትል "ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ............ ፍሥሐ ወሰላም" በማለት ልጆቿ ምዕመናን እርስ በእርሳቸው ሰላምታ በመለዋወጥ ደስታቸውን እንዲያብስሩ ታውጃለች።     ቀጣዩን እዚህ ያንብቡ ......

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም በጤና አደረሳችሁ

ብፁዕ አባታችን የትንሣኤን በዓል በተመለከተ ያስተማሩት ትምህርትና ቡራኬ

              abatachen yetinsaie

              ምን አይነት ፍቅር ነው

በሰማይና በምድር የመላውን የምናየውንና የማናየውን ሁሉ በቃሉ ፈጥሮ ካዘጋጀ በኋላ ለዚያ ሁሉ ገዢ ተመራማሪ የርሱን አምሣያ በመልኩ የፈጠረባቸው እጆቹ ተውግተው በቀራንዮ አደባባይ በመስቀል ላይ ዋሉ። (ዮሐንስ 9:7)

ሲፈጥረን ጀምሮ ዳር ድንበር የሌለው ፍቅሩ አስገድዶት በአመፃችን በበደላችን ከገባንበት የኃጢአት መቀመቅ ሊገላግለን እርሱ እራሱ በሞቱ ተቤዠን በሲዖል ተጥለው በአጋንንት ሲረገጡ የነበሩ ነፍሳትን ነፃ አወጣልን።

በአንደበቱ ሀሰት የሌለበት አምላክ ተላልፎ እንድሚሰጥና እንደሚሰቀል፤ ከሞተ በኃላ ሞትን ድል አድርጎ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሳ ለደቀመዛሙርቱ ሲናገር እንደነበረው ቀኑ ደርሶ ሰዓቱ ስለሞላና ሞት ድል ስለተነሳልን ይህን የደስታ ቀን የትንሣኤውን በዓል በየዓመቱ እንድናከብር የአምላካችን ፈቃድ ሆነ።

                      ቀጣዩን እዚህ ያንብብ...............

              ከመጋቢት መድኃኔዓለም በዓል

የመጋቢት መድኃኔዓለም አመታዊ በዓል ለሦስት ቀን በተዘጋጀ መንፈሳዊ ጉባዔ ሲካሄድ ቆይቶ እሁድ መጋቢት 30 (April 8) ቀን በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
በዓሉ ምን ይመስል እንደነበር ለመከታተል ከሥር ያስቀመጥነውን በመጫን ይመልከቱ።
                      ወደ ቪድዮው .........