መንፈሳዊ ጉባኤ
የጥምቀት በዓልን አስመልክቶ ለሦስት ቀን በስቶክሆልም ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉባኤ
በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቀቀ።
የጉባኤውን ትምህርት ለመከታተል ከታች ያስቀመጥነውን ምስል ይጫኑ።
የመድኃኔዓለም አመታዊ በዓል
የጥቅምት መድኃኔዓለም አመታዊ በዓል ለሦስት ቀን በተዘጋጀ መንፈሳዊ ጉባኤ ሲካሄድ ቆይቶ ለዚህም በዓል ምዕመናን ከጉተንበርግ እና እንዲሁም ከተለያዩ
አካባቢዋች በመምጣትና በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በአንድ ላይ በመገኘት ታቦተ ህጉ ወጥቶ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
በዓሉ ምን ይመስል እንደነበር ለማየት ከስር ያሰቀመጥነውን የምስልና የቪድዮ ሊንክ በመጫን ይመልከቱ።
የተቀሩትን የጉባኤ ትምህርት ቪድዮ ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
የቅዱስ መስቀል በዓል
እንኳን ለቅዱስ መስቀል በሰላም አደረሳችሁ። በየዓመቱ እንደምናደርገው ሁሉ ዘንድሮም የመስቀል ደመራ ከብረ በዓል በትላንታው እለት ይኽውም መስከረም አስራ ስድስት(16) ቀን
ወይም በአውሮፓውያን አቆጣጠር ሰፕቴምበር ሃያ ሰባት(27) በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
የአስራ አራተኛው መንፈሳዊ ጉባኤ
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ከሐምሌ 8 2003(ጁላይ 15 2011) ጀምሮ እስከ ሐምሌ 10 2003(ጁላይ 17 2011) ሲካሄድ የቆየው የአስራ አራተኛው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በአስደሳች ሁኔታ ተጠናቀቀ።
በብፁዕ አባታችን አባ ኤልያስ በአውሮፓ፣ በምሥራቅና ደብብ አፍሪቃ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተሰጥቶ ከተጀመረበት መጀመሪያ ቀን ጀምሮ
በተለያዩ የእግዚአብሔር ፀጋው በበዛላቸው መምህራን፣ ዘማሪያን እና መዘምራን ግሩም የሆነ መንፈሳዊ ትምህርት እና ዝማሬ በማቅረብ የጉባኤውን ታዳሚ ልዩ በሆነ መንፈሳዊ ስሜት ሲያወያይ ውልዋል።
ይህ በማናቸውም መልክ ልዩ የሆነ ከተለያየ ሃገር በመጡ ካህናት አባቶች እና ምዕመናን የተሳተፉበት ጉባኤ ምን ይመስል እንደነበር ለማየት ከታች ያስቀመጥነውን ሊንክ በመጫን ፎቶግራፎቹን ይመልከቱ።
የብፁዕ አባታችን አባታዊ ምክር

ቪድዮ
ፎቶግራፍ